የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በደሴ ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ አደረገ።

15

ደሴ: የካቲት 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ‎”አብሮነት ለበጎነት በረመዳን” በሚል መሪ መልዕክት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደሴ ዲስትሪክት የተዘጋጀ የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብር በደሴ ከተማ ተካሂዷል።

‎ባንኩ በከተማዋ በአምስቱም ክፍለ ከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ 150 የኅብረተሰብ ክፍሎች ነው ድጋፍ ያደረገው። 750 ሺህ ብር ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች ነው ድጋፍ የተደረጉት።

‎ድጋፍ የተደረገላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችም በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስለተደረገላቸው እገዛም ምሥጋና አቅርበዋል።

‎የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደሴ ዲስትሪክት ተጠባባቂ ዳይሬክተር መብራቴ ሞላ የድጋፉ ዓላማ ባንኩ ለማኅበረሰቡ ያለውን አጋርነት ለመግለጽ ታስቦ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።

‎በደሴ ከተማ የተካሄደው ድጋፍ ጅማሮ መኾኑን የገለጹት ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ በቀጣይ በተለያዩ አካባቢዎች ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ዘጋቢ:- ፊኒክስ ሀየሎም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleመንግሥት የሴቶችን መብት ለማስጠበቅ እና የውሳኔ ሰጭነት ሚናቸውን ለማሳደግ እየወሰደ ባለው ጠንካራ እርምጃ አበረታች ለውጦች መመዝገባቸው ተገለጸ።
Next articleማይክሮሶፍት ስካይፕን ሊዘጋ ነው