በወልድያ ከተማ በሚሠሩ የልማት ሥራዎች የኅብረተሰቡ ተሳትፎ እና ተባባሪነት የሚበረታታ መኾኑ ተገለጸ።

21

ባሕር ዳር: የካቲት 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች በወልድያ ከተማ እየተሠሩ ያሉ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

የአማራ ክልል ውኃ እና ኢነርጂ ቢሮ ኀላፊ ማማሩ አያሌው (ዶ.ር) የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማሟላት እየተሠሩ ያሉ የልማት ሥራዎች የሚበረታቱ መኾናቸውን ገልጸዋል።

ከተማዋን ለቱሪዝም፣ ለኢንቨስትመንት ሳቢ እና ማራኪ፣ ለኖሪዎቿም ምቹ ለማድረግ በከተማ አሥተዳደሩ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች በጥሩ ሂደት ላይ መኾናቸውን ተናግረዋል።

የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ ከተማው ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በጥሩ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። የፕሮጀክቶች ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

አብዛኞቹን ፕሮጀክቶች እስከ መጋቢት 30 2017ዓ.ም እንዲጠናቀቁ ታስቦ እየተሠራ ነው ብለዋል።

ኅብረተሰቡ በሚሠሩ የተለያዩ ልማቶች ላይ የሚያሳየው ተሳትፎና ተባባሪነት የሚያስደስት ነው ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው በቀጣይም ማኅበረሰቡ በዕውቀት በገንዘብ እና በጉልበት የሚችለውን በማድረግ የኮሪደር ልማቱ ላይ እንዲሳተፍ ጠይቀዋል።

ከወልድያ ከተማ ኮምዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች የሰላሳ ሜትር የቀለበት መንገድ ፕሮጀክት፣የንግድ ማዕከል ግንባታ፣ የቤተ መጻሕፍት ግንባታ እና የኮሪደር ልማት ሥራን ጎብኝተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የኬኛ ቤቭሬጅ ፋብሪካን ተመልክተዋል።
Next articleበምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል ኀላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ መልእክት:-