
ባሕር ዳር: የካቲት 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ባሕር ዳር ኅብረተሰቡ በሚዝናናባቸው መናፈሻዎች፣ ብስክሌት በነጻነት ማሽከርከር በሚያስችሉ ሰፋፊ መንገዶች እየተዋበች ነው ብለዋል።
ጣናን ከልሎ የነበረው ጢሻ ተገላልጦ የሐይቁ ድብቅ ውበት ፍንትው ብሎ መመልከት ሀሴትን ያጎናፅፋል ነው ያሉት።
ለአገልግሎት ክፍት የሆኑትም ኾነ በሂደት ላይ የሚገኙ የሕዝብ መዝናኛ ሥፍራዎች፣ በዘላቂነት ለረጅም ዓመታት እንዲያገለግሉ ኅብረተሰቡ በባለቤትነት መንፈስ ሊጠብቃቸው እና ሊንከባከባቸው ይገባል ብለዋል በመልዕክታቸው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!