“የሰላም እና የመልካም አሥተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ መመለስ ይገባል” አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ

20

ባሕር ዳር: የካቲት 25/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር የክልል ምክር ቤት ተመራጮች የመራጭ ተመራጭ መድረክ ተካሂዷል።

የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ በመንግሥት መሪነት እና በማኅበረሰቡ ንቁ ተሳትፎ የከተማዋን የልማት፣ የሰላም እና የመልካም አሥተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መመለስ ይገባል ብለዋል።

የሕዝብ ወኪሎች ውክልናቸውን በአግባቡ ለመወጣት እየሠሩ ስለመኾኑም ገልጸዋል። የዜጎችን የልማት፣ የሰላም እና የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ጥያቄዎች በውይይት እና በሃሳብ የበላይነት መፈታት ይኖርባቸዋልም ነው ያሉት።

መንግሥት፣ የፀጥታ መዋቅሩ እና ማኅበረሰቡ ተቀናጅተው በሠሩት የተጠናከረ ተግባር ለአካባቢው ሰላም መረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው ተገልጿል።

የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ሙሐመድ አሚን የሱፍ የከተማዋን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ በፌደራል መንግሥት እና በከተማ አሥተዳደሩ ትብብር በርካታ ፕሮጀክቶች እየተሠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበጎንደር ከተማ 2 ሺህ 600 ነጋዴዎች በአዲስ ወደ ንግድ መረቡ እንዲገቡ ተደርጓል።
Next article“የሥልጠናውን ውጤት ታች ወርዶ በተግባር መፈጸም ይገባል” ማማሩ አያሌው (ዶ.ር)