
ባሕር ዳር: የካቲት 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በምሥራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ማርቆስ ከተማ በሕገ ወጥ መንገድ በመጋዘን ላይ የነበረ የአፈር ማዳበሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉን የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ሚሊሻ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
የአፈር ማዳበሪያው የተያዘው በማኅበረሰቡ ጥቆማ መኾኑም ተገልጿል።
በከተማዋ የሚፈጸሙ መሰል ወንጀሎችን ለመከላከል ማኅበረሰቡ ለፀጥታ ኅይሉ እያደረገ ያለውን ጥቆማ አጠናክሮ እንዲቀጥል መጠየቁን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
