በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ባቲ ወረዳ የቀበሌ መሪዎችን ለማብቃት ያለመ ሥልጠና እየተሰጠ ነው።

28

ከሚሴ: የካቲት 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ባቲ ወረዳ ለቀበሌ መሪዎች “ቀበሌዎቻችንን በማጽናት ሁለንተናዊ ዕምርታ እናስመዘግባለን” በሚል መሪ መልዕክት ለሦስት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እየተሰጠ ነው።

ሥልጠናው በጸጥታ፣ በፖለቲካ፣ በልማት እና በመልካም አሥተዳደር ዙሪያ ያተኮረ ሲኾን፣ የክልሉ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ያቀረቡት የቪዲዮ ሥልጠናን ጨምሮ የተለያዩ ተዛማጅ የትምህርት ሰነዶች ቀርበዋል።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ እና ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኀላፊ አህመድ ሙህዲን የሥልጠናውን ሰነድ ሲያስተዋውቁ ከዚህ ቀደም የተካሄደውን የፓርቲ ጉባኤ በማስታወስ የሥልጠናውን ዓላማ እና ዋና ጭብጥ አብራርተዋል።

የባቲ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ መሀመድ አብዱ የረመዳን ወርን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ሥልጠናው በወረዳው የሚገኙ ቀበሌዎች ሰላምን ለማረጋገጥ፣ የሕዝብን ማኅበራዊ እረፍት ለማስጠበቅ እንዲሁም የልማት እና የመልካም አሥተዳደር ሥራዎችን ለማከናወን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ መኾኑን ገልጸዋል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ጤና መምሪያ ኀላፊ ኡስማን አሊ የቀበሌ መሪዎች ሕዝብን በቀጥታ የሚያገኙ እና ለጠንካራ መንግሥት የሕዝብ ይሁንታ የሚያስገኙ በመኾናቸው በየቀበሌው ሰላምን ማስፈን እና ማጽናት አስፈላጊ መኾኑን አስገንዝበዋል።

ሥልጠናው መሪዎችን በሁሉም ዘርፍ አቅማቸውን በመገንባት ተቀባይነት ያላቸው የሥራ ኀላፊዎችን ለመፍጠር ያለመ መኾኑ ተገልጿል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በቀበሌዎች ላይ የሚካሄዱ የውይይት ሀሳቦች እና ስትራቴጂዎች ቀበሌዎችን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ” የሀራ ከተማ አሥተዳደር
Next articleየፋርጣ ወረዳ ለቀበሌ መሪዎች ሥልጠና እየሠጠ ነው።