“ቀበሌዎቻችን የከተማችን ሁለንተናዊ መሰረቶች ናቸው” የወልድያ ከተማ አሥተዳደር

19

ወልድያ: የካቲት 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) “ቀበሌዎቻችንን በማፅናት ሁለንተናዊ እምርታ እናስመዘግባለን” በሚል መሪ መልዕክት የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ለቀበሌ መሪዎች ሥልጠና እየተሰጠ ነው።

የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ ቀበሌዎቻችን የከተማችን ሁለንተናዊ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በመኾኑም ሰላምን ለማፅናት ቀበሌዎች ላይ እግርን መትከል ወሳኝ መኾኑን አስረድተዋል።

የሥልጠና ተሳታፊዎች የቀበሌያቸውን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ሰላምን በሕዝባቸው እንዲያሰርፁ አደራ ብለዋል።

በሥልጠናው ላይም በነፃነት ሀሳብ እንዲያጋሩ እና ለተግባራዊነቱ ቁርጠኛ ኾነው እንዲሳተፉ አሳስበዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous article“በክልሉ ያልተቋጨውን ሕግ የማስከበር ሥራ ለማጠናቀቅ መንግሥት ዝግጅት አድርጓል” የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
Next article“በቀበሌዎች ላይ የሚካሄዱ የውይይት ሀሳቦች እና ስትራቴጂዎች ቀበሌዎችን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ” የሀራ ከተማ አሥተዳደር