
ባሕር ዳር: የካቲት 18/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች የባሕር ዳር ከተማን የልማት ሥራዎች እየጎበኙ ነው።
በጉብኝቱ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይንዓለም ንጉሤ፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አሥተባባሪ እና የከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኀላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ.ር)፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ፣ የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።
የሥራ ኀላፊዎቹ የባሕር ዳር የኮሪደር ልማት እና ሌሎች የልማት ሥራዎችንም ይጎበኛሉ።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
