በደቡብ ጎንደር ዞን በመስኖ ልማት ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል።

34

ደብረታቦር: የካቲት 17/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ እና ሊቦ ከምከም ወረዳዎች በመስኖ እየለማ ያለ ሰብል ተጎብኝቷል።

በደቡብ ጎንደር ዞን በተያዘው የምርት ዘመን ከ47 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን የዕቅዱን 93 በመቶ ማልማት እንደተቻለ የዞኑ ዋና አሥተዳዳሪ ጥላሁን ደጀኔ ለአሚኮ ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ 29 ሺህ 400 ሄክታር መሬት በቆላ ስንዴ ለምቷል ነው ያሉት።

በተያዘው የመስኖ ሥራ በሁሉም የሰብል አይነቶች ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም አብራርተዋል።

ዘጋቢ፦ አስፋው ሙቀት

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከ500 ሺህ በላይ ለሚኾኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን የአማራ ክልል ሥራና ሥልጠና ቢሮ ገለጸ።
Next articleከ600ሺህ በላይ ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙ ተገለጸ።