
ባሕር ዳር: የካቲት 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) “ከቃል እስከ ባሕል” በሚል መሪ መልዕክት በሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ ውይይት መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፣ የአፋር ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሐፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል መሐመድ አሕመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥ ሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ መኾናቸውን ከብልጽግና ፓርቲ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!