ሰኔ ውስጥ በኢትዮጵያ የፀሐይ ግርዶሽ ይከሰታል፡፡

828

ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 29/2012 ዓ.ም (አብመድ) በኢትዮጵያ፣ ፓኪስታን፣ ህንድ እና ማዕከላዊ አፍሪካ ሰኔ 14 ቀን 2012 ዓ.ም ቀለበታዊ የፀሐይ ግርዶሽ እንደሚከሰት የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡

በኢትዮጵያ የፀሐይ ግርዶሹ ከምዕራብ እስከ ሰሜን ምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍል በተለይም በላልይበላ አካባቢ ከጠዋቱ 12፡45 እስከ ቀኑ 6፡33 እንደሚቆይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ሰሎሞን በላይ (ዶክተር) ገልፀዋል፡፡

እንደ ኢብኮ ዘገባ በዕለቱም ከረፋዱ 3፡40 አካባቢ ለተወሰኑ ሴኮንዶች ጨለማ እንደሚፈጠርም ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡

Previous articleከሦስት ዓመት በፊት የተከሰተው እና በየጊዜው ብቅ እያለ በሰብል ላይ ጉዳት የሚያደርሰውን ሁሉን አውዳሚ ተምች በመደበኛ ተባይነት ፈርጆ እየሠራ መሆኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡
Next articleየአገው ብሔራዊ ሸንጎ ዓላማውን እየሳተ በመሆኑ ድርጅቱን መልቀቃቸውን ምክትል ሊቀመንበር የነበሩት አቶ አዲሱ መኮንን አስታወቁ።