ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች የመገጭ ግድብ ፕሮጄክትን ጎበኙ።

41

ባሕር ዳር: የካቲት 13/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች የመገጭ ግድብ ፕሮጄክትን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪሰ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሙዓዘጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ፣ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው እና የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው ተገኝተዋል።

በጉብኝታቸውም ፕሮጄክቱ በተያዘለት ጊዜ እየተከናወነ መኾኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል። የመገጭ ግድብ በልዩ ትኩረት እና ክትትል እየተሠራ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው። ፕሮጄክቱ ሲጠናቀቅ የጎንደር ከተማ አሥተዳደርን የንጹሕ መጠጥ ውኃ ችግር እንደሚቀርፍ ይጠበቃል። ግድቡ ከንጹሕ መጠጥ ውኃ ባሻገር ለመስኖ ልማት አገልግሎት ይሰጣል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ብር የተመደበላቸው ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መኾናቸውን የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገለጸ።
Next articleበበጀት ዓመቱ ከ1 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።