የአዊ ልማት ማኅበር በእንጅባራ ከተማ ያስገነባውን ባለ ስድስት ፎቅ ሁለገብ የገቢ ማስገኛ ሕንጻ አስመረቀ።

17

እንጅባራ: የካቲት 13/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ዋና አሥተዳዳሪ ቴዎድሮስ እንዳለው እና የአዊ ብሔረሰብ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሙሉዓዳም እጅጉን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

የአዊ ልማት ማኅበር ሥራ አሥኪያጅ ጌታዬ ሁነኛው ሁለገብ የገቢ ማስገኛ ሕንጻው በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሲኾን ከ94 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበታል ብለዋል።

ሕንጻው ለቢሮ፣ ለመኝታ፣ ለመሠብሠቢያ አዳራሽ፣ ለካፌ እና ለሌሎችም አገልግሎቶች የሚውሉ የተለያዩ ክፍሎችን የያዘ እንደኾነም ተናግረዋል።

የሕንጻው መገንባት ልማት ማኅበሩ የመንግሥት የልማት ክፍተቶችን ለመሸፈን ለሚያደርገው ጥረት ተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅም የሚፈጥር እንደኾነም ሥራ አሥኪያጁ ገልጸዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የተቀናጀ የሀብት አጠቃቀም ሶፍትዌር የምረቃ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።
Next articleበደብረ ማርቆስ ከተማ ሲሠለጥኑ የቆዩ የሰላም አስከባሪ እና የሚሊሻ አባላት ተመረቁ።