“የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን ማስፋፋት ለምናልመው ብልፅግና ወሳኝ ነው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

24

ባሕር ዳር: የካቲት 13/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን ማስፋፋት ለምናልመው ብልፅግና ወሳኝ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአማራ ብረታ ብረት ኢንዱስትሪና ማሽን ቴክኖሎጂ ልማት ኢንተርፕራይዝ ለብልፅግና የሚኖረውን አበርክቶ ጠቁመዋል።

በዚህም በባሕር ዳር ከተማ በኢንተርፕራይዙ የተመረቱት ስማርት ፖሎች፣ የዲች ከቨሮች እና ሌሎች ምርቶች በክልሉ እየተሠሩ ላሉ የኮሪደር ልማቶች ጥቅም ላይ መዋል መጀመራቸውን ነው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የገለጹት።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleከ31 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሠብሠቡን የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።
Next article“የእርሻ ውል ሥርዓት ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ድርሻው ከፍተኛ ነው” አቶ አጀበ ስንሻው