“የካቲት 12 ዘመን ተሻጋሪ ፅናታችንን የምናስብበት ነው” ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

34

ባሕር ዳር: የካቲት 12/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የካቲት 12 ለሀገራችን ያለንን ፍቅር እና ዘመን ተሻጋሪ የኾነ ጽናታችንን የምናሳይት ነው ሲሉ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ተናገሩ፡፡

ፕሬዝዳንቱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የካቲት 12 የመስዋዕታችንን ፋይዳ የምናስብበት ዕለት ነው ብለዋል፡፡

የካቲት 12 የሰማዕታት ቀን የኢትዮጵያውያን የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሎ፣ ለነፃነት ያለን ቀናዒነት፣ ለሀገራችን ያለንን ፍቅር፣ ዘመን ተሻጋሪ የኾነውን ጽናታችን እና የመስዋዕታችንን ፋይዳ የምናስብበት ዕለት ነውም ብለዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የሰላሙም ኾነ የልማቱ ቁልፍ ያለው በሕዝብ እጅ ነው” አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፍዬ
Next article“ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን ያቆዩት በመሥዋዕትነት ነው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ