ከ94 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ጋን አገልግሎት ጀመረ።

36

ወልድያ: የካቲት 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የክልል እና የዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ አሥተዳደር የተሠራ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ማጠራቀሚያ ጋን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎቹ በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ የተሠሩ የልማት ሥራዎችንም እየጎበኙ ነው።

ለአገልግሎት ክፍት የኾነው የውኃ ማጠራቀሚያ ጋኑ አንድ ሚሊዮን ሊትር ውኃ የማያዝ አቅም እንዳለው ተመላክቷል። ሥራው 10 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጭ የተደረገበት መኾኑም ተገልጿል። ከ94 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ነው የተባለው። ጋኑ የቆቦ ከተማን ሕዝብ የንጹህ መጠጥ ውኃ እጥረት እንደሚቀርፍ ተመላክቷል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleትርፍ እና ታሪፍን ለመቆጣጠር ኢ-“ቲኬቲንግ እየተጠቀመ መኾኑን የአማራ ክልል ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ባለሥልጣን አስታወቀ።
Next articleበጎንደር ከተማ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የከተማዋን ታሪካዊነት የሚመጥኑ መኾናቸውን የአሚኮ ጎንደር ቅርንጫፍ ሠራተኞች ተናገሩ።