የከተማዋን ኢንቨስትመንት የማነቃቃት ዓላማ ያለው ምክክር በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

41

ባሕር ዳር: የካቲት 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ ”ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት” በሚል መሪ መልዕክት ከከተማ አሥተዳደሩ ባለሀብቶች እና አጋር አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።

የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኀላፊ እንድሪስ አብዱን ጨምሮ የክልል እና የከተማ አሥተዳደሩ መሪዎች ተገኝተዋል።

የምርት አውደ ርዕዩን የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኀላፊ እንድሪስ አብዱ እና የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው አስጀምረውታል።

አምራቾችም ምርቶቻቸውን ለእይታ እና ለሽያጭ አቅርበዋል።

ውይይቱ የከተማዋን ኢንቨስትመንት የማነቃቃት ዓላማ ያለው ሲኾን የክልል እና የከተማ አሥተዳደሩ ከፍተኛ መሪዎች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ፦ ዋሴ ባየ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ችግር እንዲፈታላቸው የመካነ ሰላም ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ።
Next articleበሦተኛው ዙር ከ3ሺህ 600 በላይ ተማሪዎችን መመዝገብ መቻሉን የምዕራብ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።