የክልሉ መሪዎች የጋሸና ከተማ ሁለገብ የቢሮ አገልግሎት መስጫ ሕንጻ ግንባታን አስጀመሩ።

46

ወልድያ: የካቲት 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል እና የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች በሰሜን ወሎ ዞን የጋሸና ከተማ አሥተዳደር ሁለገብ የቢሮ አገልግሎት መስጫ ሕንጻ ግንባታን አስጀምረዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አራጌ ይመር እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ሥራውን አስጀምረዋል።

ሕንጻው ባለስምንት ወለል ሲኾን በከተማ አሥተዳደሩ ሙሉ ወጭ የሚገነባ መኾኑን የጋሸና ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ፀጋ ውቤ ገልጸዋል።

የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ይህ የመሠረተ ልማት የሥራ ማስጀመሪያ ውጤት ላይ ሲደርስ ድርብ ደስታ ይኾናል ብለዋል።

ሥራው ተጠናቅቆ ለምረቃ ሲበቃ ውጤታማ መኾኑ እንደሚረጋገጥ ገልጸው ለዚህም በትጋት ልትሠሩ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article254 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ እየለማ መኾኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡
Next articleከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በጉባላፍቶ ወረዳ የሳንቃ ጤና ጣቢያን እየጎበኙ ነው።