ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በፍላቂት ከተማ ነዋሪዎች ጋር እየተወያዩ ነው።

40

ወልድያ: የካቲት 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የክልል እና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በፍላቂት ከተማ በሰላም፣ በልማት እና በመልካም አሥተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ በሰሜን ወሎ ዞን ከፍላቂት ገረገራ ከተማ አሥተዳደር እና ከመቄት ወረዳ ከተውጣጡ ነዋሪዎች ጋር ውይይ እያደረጉ ነው።

ውይይቱን የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኀላፊ ፍስሃ ደሳለኝ እና የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አራጌ ይመር እየመሩት ነው።

በውይይቱ ሌሎች ከፍተኛ የክልል እና የዞን የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከ169 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ማግኘቱን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
Next articleበሀገራዊ ምክክር ሂደቶች እየታዩ ያሉ ተጓዳኝ ውጤቶች