በኅብረተሰብ ተሳትፎ እና በመንግሥት በጀት የተገነባ ባለ አምስት ወለል ሕንፃ ተመረቀ።

59

ወልድያ: የካቲት 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል እና የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች በሰሜን ወሎ ዞን ጋዞ ወረዳ የተሠሩ የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።

በጉብኝቱ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ ምክትል ርእሰ መሥተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ጨምሮ ሌሎች የክልል እና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎቹ በ132 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የጋዞ ወረዳ አሥተዳደር ምክር ቤት ቢሮ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

ሁለገብ የቢሮ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ የተገነባው ሕንፃ ባለ አምስት ወለል ነው። 1 ሺህ 200 ሰው የሚይዝ ከፍተኛ አዳራሽ እና ተጨማሪ አነስተኛ አዳራሾች እንዳሉትም ተመላክቷል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየተሠሩ የልማት ሥራዎች በችግርም ውስጥ ኾኖ መሥራት እንደሚቻል ያሳዩ መኾናቸውን አፈጉባዔ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ።
Next article“38ኛው የአፍሪካ ኅብረት መደበኛ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቅቋል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)