ባሕር ዳር: የካቲት 08/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ጋቪ- ቫክሲን አሊያንስ ከተባለ የጤና አጋር ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳኒያ ኒሽታር ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸው የኢትዮጵያን የክትባት ጥረቶችን በማጠናከር፣ የጤና ሥርዓትን የመቋቋም አቅም እና በጤናው ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን እቅድ እድገት ላይ መክረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኤክስ ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሠሩም መወያየታቸውንም ገልፀዋል፡፡
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!