ባሕር ዳር: የካቲት 08/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በየዓመቱ የሚቀያየረው የአፍሪካ ኅብረት ሊቀ-መንበርነትን በ2024 ስትመራ የነበረችው ሞሪታኒያ ስልጣኑን ለአንጎላ አስረክባለች።
የኅብረቱ ሊቀመንበር የነበሩት የሞሪታኒያው ፕሬዝዳንት ሞሃምድ ኡልድ ጋዝዋኒ ለወቅቱ የኅብረቱ ሊቀ-መንበር ሆነው ለተመረጡት የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዧ ማኑኤል ጎሳዌስ ሎሬንሶ መልካም የሥራ ዘመን ተመኝተዋል።
አንጎላ የ2025 የአፍሪካ ኅብረት ሊቀ-መንበር በመሆን ሥራዋን ጀምራለች።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!