
አዲስ አበባ: የካቲት 07/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ለመታደም የማዳጋስካር ፕሬዝዳንት አንድሪ ራጁዌሊና አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ፕሬዝዳንቱም ለተደረገላቸው አቀባበልም ምሥጋና አቅርበዋል::
ዘጋቢ፦ ሰለሞን አሰፌ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!