
ባሕር ዳር: የካቲት 06/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የጽሕፈት ቤት ኀላፊ አባንግ ኩሙዳን የተመራ ልዑክ በባሕር ዳር ጉብኝት እያደረገ ነው።
የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የሥራ ኀላፊዎች ለልዑካን ቡድኑ የእንኳን ደኅና መጣችሁ አቀባበል መልዕክት አስተላልፈዋል።
ልዑኩ በቆይታው ሀገራዊ የወጣቶች የፖለቲካ፣ የምጣኔ ሀብት እና የማኅበራዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነትን ለማጎልበት በ2017 በጀት ዓመት በ6 ወራት በወጣቶች ክንፍ የተሠሩ ሥራዎች፣ ስኬቶች እና ጉድለቶችን ይገመግማል። የቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚያስቀምጥም ይጠበቃል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ መሪዎች ፣ የሁሉም የክልል እና የከተማ አሥተዳደሮች የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊዎች ይሳተፋሉ።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!