በ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ጥሩ ውጤት እንዲመዘገብ እየሠራ መኾኑን የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ ገለጸ።

32

ባሕር ዳር: የካቲት 05/2017 ዓ.ም(አሚኮ) የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ የ2017 የስድስት ወር የሥራ አፈጻጸምን እየገመገመ ነው።

በግምገማው የመምሪያው ከፍተኛ የትምህርት መሪዎች፣ ባለሙያዎች፣ ርዕሳነ መምህራን እና ሱፐርቫይዘሮች እየተሳተፉ ነው።

በባሕርዳር ከተማ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ የፈተና ዝግጅት እና አሥተዳደር ባለሙያ አበበ አያሌው በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7ሺህ በላይ የ6ኛ እና ከ8ሺህ በላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ጥሩ ውጤት እንዲመዘገብ እየተሠራ ነው ብለዋል።

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ለመውሰድ ከተመዘገቡት ከ6ሺህ 504 በላይ ተማሪዎች መካከል 35 በመቶ የሚኾኑት ከ50 በመቶ በላይ ውጤት አምጥተው ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ እየተሠራ መኾኑንም ተናግረዋል።

ዘጋቢ:- ሙሉጌታ ሙጨ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበደረሰው የእሳት አደጋ 18 ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን የደብረ ብርሃን ከተማ ፖሊስ አስታወቀ።
Next articleርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለምክር ቤቱ ስለ በግብርናዎው ክፍለ ኢኮኖሚ ካነሷቸው አንኳር ጉዳዮች በጥቂቱ፡-