
ባሕርዳር: የካቲት 05/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአሜሪካ የኢፌዴሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱዓለም የሹመት ደብዳቤያቸውን ቅጂ በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ለፕሮቶኮል ተጠባባቂ ሹም አቢ ጆንስ አቅርበዋል።
አምባሳደሩ በሁለቱ ሀገራት መካከል ረጅም ጊዜ የቆየ ግንኙነት መኖሩን ተናግረዋል። በዋሽንግተን የኢትዮጵያ ኢምባሲ የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው በቀጣይ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሠሩ ገልጸዋል።
በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ለፕሮቶኮል ተጠባባቂ ሹም አቢ ጆንስ አምባሳደሩ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር በሚያከናውኑት ተግባራት አስፈላጊውን ሁሉ ትብብር እንደሚያደርጉላቸው ቃል ገብተዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!