” በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የተሟላ ግንዛቤ በመያዝ ለሕዝብ ተጠቃሚነት መሥራት ይገባል” የደብረታቦር ከተማ ከንቲባ ደሴ መኮንን

29

ባሕር ዳር: የካቲት 04/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረታቦር ከተማ አሥተዳደር የከተማ አሥተዳደሩ መሪዎች በተገኙበት በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛው መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና የቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የሚመክር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ መልዕክት ያስተላለፉት የደብረታቦር ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ደሴ መኮንን ውይይቱ መሪዎች እና አባላት በአጀንዳዎቹ ዙሪያ የጠራ አቋም በመያዝ የተወሰኑ ውሳኔዎች ላይ ዕውቅና እንዲኖራቸው፣ የቀጣይ አቅጣጫዎችን የጋራ በማድረግ የሀገርን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በፈተናዎች ሳይበገር በርካታ ድሎችን ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል። ” የተገኙ ለውጦችን ማስቀጠል እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች የተሟላ ግንዛቤ በመያዝ ለሕዝብ ተጠቃሚነት እና ለሀገር ብልጽግና መሥራት እንደሚገባ” አመላክተዋል።

ከደብረ ታቦር ከተማ አሥተዳደር ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የደብረታቦር ከተማ አሥተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ደበበ አክሎግ በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችን እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን አቅርበዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአቶ አደም ፋራህ በዓለም የመንግሥታት ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ነው።
Next articleምክር ቤቶች የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ሀገራዊ ኀላፊነታቸውን እንዲወጡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ አሳሰቡ።