በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮሪደር ልማት በሰባት ከተማ አሥተዳደሮች ተጀምሯል።

48

ባሕርዳር: የካቲት 03/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክልል ማዕከል በሆኑ ከተሞች እና በሌሎች የዞን ማዕከላት የኮሪደር ልማት ተጠናክሮ እየተሠራ ነው።

ከፌዴራል፣ ከዞን፣ከከተማ አሥተዳደር እና ከኅብረተሰብ ተሳትፎ በተገኝ ሀብት በስምንት ከተማ አሥተዳደር እየተሠራ ነው ተብሏል።

ወላይታ ሶዶ፣ አርባ ምንጭ፣ ዲላ፣ ሳውላ፣ ጂንካ፣ ካራት እና ይርጋ ጨፌ ከተሞች በኮሪደር ልማት 41 ኪሜ መንገድ፣ 26 ሄክታር የአረንጓዴ ቦታዎች እና የፓርክ ልማት፣ 9 የልጆች መጫወቻ ቦታዎች ፣11 ኪሜ የመንገድ ዳር መብራትና ሕንጻ የማስዋብ ሥራ እና 0.18 ሄክታር የአደባባይ ቦታዎች የማልማት ሥራ 3 ፋውንቴን ሥራዎች ተሠርተዋል ነው የተባለው።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሐፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው አንዳንዶች የመጀመሪያ ዙር አጠናቀው ሁለተኛ ዙር ጀምረዋል። አርባምንጭ ከተማ፣ የእግረኛ መንገድ በአንድ በኩል፣ የብስክሌት መንገድ ፣ አረንጓዴ ስፍራ እና የመብራት ስማርት ላይት ያካተተ ሥራ ተከናውኗል ነው የተባለው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአካታችነትን መርህ አድርጎ እየሠራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ገለጸ፡፡
Next article“የሴፍቲኔት መርሐግብር ሥራ ፈጣሪነትን በማጠናከር የራስን ችግር በራስ የመፍታት ልምምድ የታየበት ነው” ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት