የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ምክር ቤት ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

33

ሰቆጣ: ጥር 30/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 29ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

ምክር ቤቱ በጉባዔው የ28ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤን፣ የ2017 ዓ.ም የስድስት ወራት የአሥፈጻሚውን ዕቅድ ክንውን ሪፖርት፣ የ2017 ዓ.ም የስድስት ወራት ኦዲት እና የሥርዓተ ጾታ ሪፖርት፣ የ2017 ዓ.ም የስድስት ወራት የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን የአፈጻጸም ሪፖርት እና የሚቀርቡ ሹመቶችን መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

ጉባኤው ለሁለት ተከታታይ ቀናት ይቆያል ተብሏል።

ዘጋቢ: ደጀን ታምሩ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ የሚመክር መድረክ እያካሄዱ ነው።
Next articleለ2017/18 የምርት ዘመን 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት መታቀዱን ግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።