የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በጎንደር እየተገነቡ ያሉ የመሠረተ ልማቶች ሥራዎችን ለመመልከት ጎንደር ከተማ ገብተዋል።

43

ጎንደር: ጥር 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ ሚኒስቴር ድኤታዎች፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን የሥራ ኀላፊዎች ናቸው ጎንደር ከተማ የገቡት።

በቆይታቸውም በጎንደር ከተማ በመልማት ላይ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን ምልከታ የሚያደርጉ ሲኾን በከተማ የልማት ተግባራት ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ዘጋቢ፦ ያየህ ፈንቴ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ከተለያዩ ተቋማት ጋር ተናቦ እየተሠራ ነው።
Next articleየኢንዱሥትሪ እና ከተማ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት ሥራ እየገመገመ ነው።