የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዚን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

25

ባሕር ዳር: ጥር 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ጀስቲስ ፎር ኦል በትብብር በመሥራት የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርአቱ ውጤታማነትን ማደበር የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

በተለያዩ ደረጃዎች የሚደረጉ የሰው ሀብት አቅም ግንባታ ሥራዎች ፣ የጉዳዮች ፍሰት አሥተዳደር ፣ የሕግ ጥናት ፣ ምርምር እና ረቂቅ ዝግጅት ፣ አማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴዎች ማጠናከር ፣ የዳኞች እና የፍትሕ አካላት ትብብር ላይ የሚተገበሩ ሥራዎች ፣ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ፣ መዝገቦችን ማጥራት ፣ የኅብረተሰብ ተሳትፎ ማሳደግ እና የፍትሕ ሥርአቱን ተዓማኒነት ማጠናከር ላይ በጋራ ለመሥራት ነው ስምምነት የፈጸሙት።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው እና የጀስቲስ ፎር ኦል ዋና ሥራ አስኪያጅ ፓስተር ዳንኤል ገብረሥላሴ ናቸው፡፡

ከአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ስምምነቱ የፍርድ ቤቱን የሰው ኃይል እና አገልግሎት አሰጣጥን በማጠናከር የፍትሕ አሥተዳደር ሥርዓት ግንባታ ላይ ትልቅ ውጤት እንደሚያመጣ ተገልጿል፡፡

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአራት ኪሎ ፕላዛ የእግረኞች የውስጥ ለውስጥ ማሳለጫ መንገድ ግንባታ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት ኾነ።
Next articleበወልዲያ ቆቦ መንገድ የትራንስፖርት አገልግሎት ችግር እንዳይፈጠር ጊዜያዊ ተለዋጭ መተላለፊያ ተሠራ።