ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኾነው ተመረጡ።

54

ባሕር ዳር: ጥር 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዶክተር ዐቢይ አሕመድን የፓርቲው ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧቸዋል። ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በተያያዘ ዜና ጉባኤው አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶች አድርጎ መርጧል።
ሁለቱ ምክትል ፕሬዚዳንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ደብረ ታቦር መሀል ጀግኖች የጻፉትን ሊቆች ያነቡታል አጅባር ከሜዳው ላይ ለዓለም ይገልጡታል”
Next article“በዓሉ ቂምን የምንሽርበት፣ ፍቅርን የምናጸናበት እና አንድነትን የምናጠናክርበት ነው” ምክትል ከንቲባ ኃይለኢየሱስ ሰሎሞን