የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉበኤ ዛሬም በመካሄድ ላይ ነው።

60

ባሕር ዳር፡ ጥር 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ትናንት “ከቃል እስከ ባሕል” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬም ቀጥሎ ይውላል።

በጉባኤው የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህን የእንኳን መጣችሁ መልዕክት ተከትሎ የመክፈቻ ንግግሩን የፓርቲው ፕሬዝዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) አድርገዋል።

የፓርቲው ፕሬዝዳንት በንግግራቸው የፓርቲውን የአምስት ዓመታት ስኬታማ ጉዞዎች የዳሰሱ ሲሆን፤ በቀጣይም ፓርቲው ሊያካናውናቸው ያሰባቸውን ጉዳዮች አመላክተዋል።

በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ የተጋበዙት የተለያዩ ሀገራት የእህት ፓርቲዎች ተወካዮችም በጉባኤው መክፈቻ ላይ መልዕክታቸውን እንዳስተላለፉም ከፓርቲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ማኅበረሰቡ ፍፁም የሰላም አየር አስኪተነፍስ ድረስ ሕግ የማስከበር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል” የምዕራብ ጎጃም ዞን
Next articleየብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ እየተወያየ ይገኛል።