በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ የእህት ፓርቲ ከፍተኛ መሪዎች ያስተላለፉት ዋና ዋና መልዕክት፦

14

✍️ “ኢትዮጵያ ምንጊዜም የምስራቅ አፍሪካ ምሰሶ ነች”

የጅቡቲው ፒፕልስ ራሊ ፎር ፕሮግረስ ፓርቲ ዋና ጸሐፊ ኢልያስ ሙሳ ዳዋሌ

✍️ “የኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት መንፈስ ለፀረ ቅኝ ግዛት እና አፓርታይድ ሥርዓት ትግል እንዲቀጣጠል አድርጓል”

የዚምባቡዌው ዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ የውጭ ግንኙነት ዋና ጸሐፊ ሲምበርሼ ሙቤንጌግዊ

✍️ “የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሃሳቦች የኢትዮጵያን ብቻ ሳይኾን የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ ይበጃሉ”

የተርኪዬ ኤኬ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዛፈር ሲራካያ

✍️ “ጉባዔው ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት አሻጋሪ እንደሚሆንና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ቦታ እንደሚያስቀጥል ባለሙሉ ተስፋ ነኝ”

የዩናይትድ ሩስያ ፓርቲ ሱፕሪም ካውንስል ቢሮ አባልና የሩስያ ፌዴሬሽን ሴናተር አንድሬ ክሊሞቭ

✍️ “በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳል የአመራርነት ጥበብ ኢትዮጵያ በፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች ትገኛለች”

የታንዛኒያው ቻማ ቻማ ፑንዱዚ ፓርቲ ዋና ጸሀፊ ኢማኑኤል ቺምቢ

✍️ “ከሁለቱ አገራት ጠንካራ ግንኙነት ባለፈ በፓርቲ ለፓርቲ መካከል የትብብር ግንኙነቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል”

የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር ፓርቲ ዋና ፀሐፊ ዌላርስ ጋሳማጌራን

✍️ “ብልጽግና ፓርቲ ቃል የገባቸውን ተግባራት የፈጸመበት መንገድ እጅግ የሚደነቅ እና ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው”

የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ ዋና ጸሀፊ ፒተር ላም

✍️ “የናይጀሪያና የኢትዮጵያ ግንኙነት በመከባበርና በጋራ እሴት ላይ የጸና ነው”

የናይጄሪያው ኤፒሲ ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር አልሀጅ አሊቡካር ዳሎሪ

✍️ “በአፍሪካ የአንድነት መሰረት እንዲጸና ልማትና ብልጽግና እንዲረጋገጥ በማድረግ ኢትዮጵያ የላቀ ሚናዋን እየተወጣች ነው”

የደቡብ አፍሪካው ናሽናል ኮንግረንስ ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባል ኑዶሎ ኪቤት

Previous articleየእንስሳት ሃብትን ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ነው።
Next article“ማኅበረሰቡ ፍፁም የሰላም አየር አስኪተነፍስ ድረስ ሕግ የማስከበር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል” የምዕራብ ጎጃም ዞን