በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ1 ሺህ 400 ሊትር በላይ ቤንዚን ተያዘ።

37

ገንዳውኃ: ጥር 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በምዕራብ ጎንደር ዞን በገንዳውኃ ከተማ አሥተዳደር በሕገ ወጥ መንገድ ተዘዋውሮ ሊሸጥ ተብሎ የተቀመጠ ከ1 ሺህ 400 ሊትር በላይ ቤንዚን በተደረገ በማኅበረሰቡ ትብብር እና በጸጥታ ኃይሉ ፍተሻ መያዙን የገንዳውኃ ከተማ አሥተዳደር ንግድ እና ገቢያ ልማት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

የገንዳውኃ ከተማ አሥተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽሕፈት ቤት ምክትል ኀላፊ ወይዘሮ ሙሉዬ አየልኝ እንደገለጹት ማኅበረሰቡ ባደረገው ትብብር እና የጸጥታ ኃይሉ ባደረገው ፍተሻ ተይዟል ነው ያሉት።

በከተማ አሥተዳደሩ ተዘዋውሮ በጥቁር ገበያ ሊሸጥ ተብሎ በዝግጅት ላይ እንደነበርም ኀላፊዋ ተናግረዋል።

ምክትል ኀላፊዋ አክለውም ማኅበረሰቡ ላደረገው ትብብር አመስግነው ቀጣይም እንዲህ ዓይነት ወንጀል ሲያጋጥም ጥቆማ እንዲሠጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ኢትዮጵያ በፈጣን ዕድገት ላይ ናት” አቶ አደም ፋራህ
Next articleአምባሳደሮች ለኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕዝብ በታማኝነት የማገልገል ኀላፊነታቸውን እንዲወጡ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አሳሰቡ።