“የአገው ፈረሰኞች በዓል የታሪካችን እና የአብሮነታችን መገለጫ ነው” ሸዊት ሻንካ

43

ባሕር ዳር: ጥር 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ዛሬ እየተከበረ የሚገኘውን 85ኛውን የአገው ፈረሰኞች ማኅበር ምስረታ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሚኒስትሯ “የአገው ፈረሰኞች በዓል ፌስቲቫል ታሪካችንን፣ አብሮነታችንን፣ ባሕላችንን አስተሳስሮ በማቆየት ለዘመናት የኖረ የማኅበረሰባችን እሴት ነው” ብለዋል።

እሴቱን መጠበቅ እና ማልማት እንደሚያስፈልግ ገልጸው በዓሉን ባሕላዊ እሴቶቻችንን በማዳበር፣ በመጠበቅና አብሮነታችንን ለዓለም በማሳየት ልናከበር ይገባል ብለዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየፈረሰኞች በዓል የአገው ሕዝብ ለሀገሩ ክብር ዋጋ የከፈሉትን ሁሉ የሚያስታውስበት ነው።
Next article‘’ የአገው ፈረሰኞች በዓል የጀግኖች አባቶቹን ታሪክ እየዘከረ እና ትውልድ እየቀረጸ ነው” አየለ አናውጤ (ዶ.ር)