“ሚስ አገው” ዛሬ ከቆይታ በኃላ ትታወቃለች።

63

እንጅባራ: ጥር 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በ85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማኅበር ዋዜማ ደምቋል።ከድምቀቶቹ መካከል “ሚስ አገው” ወይም የአገው ቆንጆ የቁንጅና ውድድር ይገኝበታል። ይህ የቁንጅና ውድድር ለቀጣይ አንድ ዓመት ያህል የብሔረሰቡ የባሕል አምባሳደር በመኾን የምታገለግለዋ ቆንጆ ሴት ትታወቅበታለች።

በመርሐ ግብሩ ላይ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ፣ የክልል እና የፌዴራል መንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ይታደማሉ።

የቁንጅና ውድድሩን የአሚኮ ጋዜጠኛ እና ደራሲ ምንችል እንግዳ፣ ተዋናይት መስከረም ነጋ እና ተዋናይ እና ደራሲ ደሳለኝ መኩሪያ በዳኝነት ሊመሩት ተሰይመዋል። ከደቂቃዎች በኋላ ሚስ አገው ትለያለች።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“እየተከናወኑ ያሉ መሠረተ ልማቶች የነዋሪዎችን ፍላጎት የሚመጥኑ ናቸው” ኢንጅነር አይሻ መሐመድ
Next article“ወይዘሪት አገው” የቁንጅና ውድድር መካሄዱን ቀጥሏል።