“የአገው ፈረሰኞች በዓል ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኝ ከሚመለከታቸው ጋር ሁሉ የጀመርነውን ሥራ አጠናክረን እንቀጥላለን”

40

ባሕር ዳር: ጥር 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሚኒስትር ማዕረግ የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኀላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ.ር) ለአገው ፈረሰኞች በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “የተከበርከው ሕዝባችን በፍፁም ሀገር ወዳድነት መንፈስ እና የአርበኝነት ወኔ ዋጋ የከፈልክበት፣ ይህንኑ ለመዘከር እና ለማስታወስ፣ ባሕልና ቅርሱን ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ ታስቦ ለተቋቋመው 85ኛው የአገው ፈረሰኞች ክበረ በዓል በሠላም አደረሣችሁ አደረሠን እላለሁ” ነው ያሉት።

ይህ ታላቅ ክብረ በዓልም የሕዝባችንን ዕሴት፣ ባሕልና ወግ ጠብቆ እንዲዘልቅ የሚያደርግ ነው ያሉት ኀላፊው በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ በጉልህ እንዲታወቅና ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኝ ከሚመለከታቸው ጋር የጀመርነውን ሥራ አጠናክረን የምንቀጥል መኾኑን ስገልፅ በታላቅ ደስታና ኩራት ጭምር ነው ብለዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይመጡ በማድረግ የሚገኝ ድልም ሆነ ዕድል የለም”የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
Next articleየደቡብ ሱዳን ሕዝቦች ነጻነት ንቅናቄ ዋና ጸሐፊ ፒተር ላም ቦዝ በብልጽግና ፓርቲ ጉባዔ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡ።