በወቅታዊ የጸጥታ ችግር ውስጥ ኾኖም ጥሩ ሥራ መሥራቱን የአማራ ክልል ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ገለጸ።

33

ባሕር ዳር: ጥር 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።

በግምገማው የአማራ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሠብሣቢዎች ተገኝተዋል።

የአማራ ክልል ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቤል ፈለቀ ባለፉት ስድስት ወራት መሠረተ ልማትን በመገንባት፣ ዲጂታላይዜሽን እና ኦቶሚሽንን በማስረጽ፣ ተቋማዊ መስተጋብር እና ትስስር በመፍጠር ረገድ አበረታች ሥራዎችን ማከናዎን ተችሏል ብለዋል።

በወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት ከዞኖች ጋር የተሟላ መረጃ መለዋወጥ እና ወደ ታችኛው እርከን ተንቀሳቅሶ ለመሥራት አስቸጋሪ እንደነበር አንስተዋል።

ባለፈው ተመሳሳይ ዓመት የኮሚሽኑ አፈጻጸም 36 በመቶ የነበረ ሲኾን ዘንድሮ በችግር ውስጥ ኾኖም 72 በመቶ ፈጽሟል ነው የተባለው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleምክር ቤቱ የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ።
Next articleመዲናዋን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የተሠሩ ሥራዎች የሚደነቁ መሆናቸውን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።