የብልጽግና ፓርቲ የጉባኤ ተሳታፊዎች በመዲናዋ የሚገኙ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው።

34

ባሕር ዳር : ጥር 22/2017 ዓ.ም(አሚኮ) ከጥር 23 አስከ 25 በሚካሄደው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የሚሳተፉ የፓርቲው ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡ እና በመገንባት ላይ የሚገኙ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው።

አዲስ አበባ የነዋሪዎቿን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ የሚያዘምኑ የመሠረተ ልማት አውታሮችን እና የኑሮ ውድነቱን የሚያቃልሉ ፕሮጀክቶችን መመልከታቸውን ጎብኚዎቹ ተናግረዋል።

“ከቃል እስከ ባሕል” በሚል መሪ መልዕክት በሚካሄደው የፓርቲው መደበኛ ጉባኤ ላይ 1ሺህ 700 በድምጽ የሚሳተፉ የፓርቲው መሪዎችን ጨምሮ የተለያዩ የኀብረተሰብ ክፍሎች እና የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች እንደሚሳተፉ ኢቢሲ ዘግቧል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝም ሀብቶችን ለማሳደግ እየሠራ ነው።
Next articleየአገው ፈረሰኞች በዓል ታሪኩን እና ባሕሉን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ዝግጅት ተጠናቅቋል።