የጸጥታ ተቋማት የውይይት መድረክ በደብረ ብርሃን ከተማ እየተካሄደ ነው።

21

ደብረ ብርሃን: ጥር 22/2017 ዓ.ም(አሚኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን እና የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር የጸጥታ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ መድረክ በደብረ ብርሃን ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በቢሮ ኀላፊ ደረጃ የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ አማካሪ ኮሎኔል ባምላኩ ዓባይ የጸጥታ ኃይሉ የክልሉን ሰላም ለማስፈን በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን እና አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ችግሮችን በሰላም ለመፍታት መንግሥት ቁርጠኛ መኾኑንም ተናግረዋል።

ባለፉት የተግባር ሥራዎች ላይ የነበሩ ጥንካሬዎችን እና ክፍተቶችን የመለየት አና የማስተካከል ተግባር ይከወናል ነው ያሉት።

በመድረኩ የሰሜን ሸዋ ዞን ሁሉም የወረዳ፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና ከደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ሁሉም ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የጸጥታ መዋቅር ኀላፊዎች እና ባለሙያዎች እየተሳተፍ ነው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየአገው ፈረሰኞች በዓል ገበያውንም አነቃቅቷል።
Next articleእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝም ሀብቶችን ለማሳደግ እየሠራ ነው።