የተርክዬ እና የሞሮኮ ገዥ ፓርቲ አመራሮች አዲስ አበባ ገብተዋል።

30

ባሕር ዳር፡ ጥር 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የተርክዬ ኤኬ ፓርቲ እና የሞሮኮው ናሽናል ራሊ ኦፍ ኢንዲፔንደንትስ(አር ኤን አይ) ፓርቲ አመራሮች በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባዔ ለመታደም አዲስ አበባ ገቡ።

ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ” ከቃል እስከ ባሕል ” በሚል መሪ ሀሳብ ከጥር 23 እስከ 25 በአዲስ አበባ ያካሂዳል።

በጉባዔው ላይ የሚታደሙ የውጭ ሀገራት የገዥ ፓርቲ ተወካዮች አዲስ አበባ እየገቡ ነው።

በዚህም የተርክዬው ኤኬ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዛፈር ሲራካያ እና የሞሮኮው ‘ናሽናል ራሊ ኢንዲፔንደንትስ’ (አር ኤን አይ) ፖርቲ ተወካይ መሐመድ ሳዲኪ ዛሬ ዕኩለ ሌሊት ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ኢዜአ እንደዘገበው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ.ር)፣ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ለእንግዶቹ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየሩዋንዳ አርበኞች ግንባር ፓርቲ ዋና ጸሃፊ ዌላርስ ጋሳማጌራ አዲስ አበባ ገብተዋል።
Next articleየአልጄሪያ ብሔራዊ ነፃነት ፓርቲ ዋና ጸሐፊ ፕሮፌሰር አብደልከሪም ቤን መባረክ አዲስ አበባ ገቡ።