በሊባኖስ እና በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 359 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።

24

ባሕርዳር: ጥር 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሊባኖስ እና በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 359 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሷል።

በሊባኖስ በአስቸጋሪ ሁኔታ የነበሩ እና ለአደጋ የተጋለጡ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር የመመለስ ሥራ እንደቀጠለ ነው። በሳምንቱ 156 ኢትዮጵያውያን ከሊባኖስ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። በሳዑዲ ዓረቢያ የነበሩ 203 ኢትዮጵያውያንም ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገልጿል።

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያ፣ በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ሥራም እየተሠራ መኾኑም ተመላክቷል።

ከሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ከሚያዚያ 04/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ከሳዑዲ ዓረቢያ ዜጎችን የመመለስ ሥራ እስካሁን 90 ሺህ 101 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article” 38ኛው አፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤን በላቀ ደረጃ ለማስተናገድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል ” አምባሳደር ብርቱካን አያኖ
Next articleከ24 ሺህ በላይ ለሚኾኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።