የጤና ባለሙያዎች በችግርም ውስጥ ኾነው ለማኅበረሰቡ የጤና አገልግሎት እየሰጡ ነው።

24

ፍኖተ ሰላም: ጥር 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የምዕራብ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር አፈጻጸም ግምገማ እና የቀጣይ ሥራዎች መድረክ በፍኖተ ሰላም ከተማ እያካሄደ ነው።

በመድረኩ የተገኙት የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ኀላፊ ሙላት ጌታቸው ባለፉት ስድስት ወራት የጤና ባለሙያው በችግር ውስጥም ኾኖ የሙያውን መርሕ በመጠበቅ ማኅበረሰቡን እያገለገለ መኾኑን ገልጸዋል።

የማኅበረሰቡን የጤና የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል አኹንም በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ነው አቶ ሙላት የተናገሩት። በግምገማ መድረኩ ላይ የሁሉም ወረዳ የጤና ተቋማት ባለሙያዎች እና ኀላፊዎች እንዲኹም የጤና ጽሕፈት ቤት ኀላፊዎች ተሳታፊዎች ናቸው።

በመድረኩ ባለፉት ስድስት ወራት በጤናው ዘርፍ የታዩ ጥንካሬዎች እና ድክመቶች ተገምግመው በቀጣይ ሥራዎች ላይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥ ይጠበቃል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየ2025 የኢንተርኔት ልማት ኮንፈረንስ ችግሮችን ለመፍታት እና አዳዲስ መፍትሔችን ለመተግበር የሚያስችል መኾኑ ተገለጸ።
Next articleየደቡብ ጎንደር ዞን እና የደብረ ታቦር ከተማ ተወላጅ ባለሀብቶች በአካባቢያቸው የሰላም እና የልማት ሥራዎች ተሳትፎ እንዲያደርጉ ተጠየቀ።