የኢትዮጵያ የደም እና ኅብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ለክልል የደም ባንኮች ድጋፍ አደረገ።

119

አዲስ አበባ: ጥር 14/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ የደም እና ኅብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለክልል ደም ባንኮች የሕክምና መሳሪያዎች ድጋፍ አድርጓል። መሳሪያዎችንም ለክልል ጤና ቢሮ ኀላፊዎች እና ተወካዮች የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ አስረክበዋል።

12 አይነት መሳሪያዎች ማለትም እንደ ደም ማቆያ፣ መመርመሪያ እና ማጓጓዣ የሚኾኑ መሳሪያዎች ድጋፍ ተደርገዋል።

በ53ቱ የደም ባንኮች ለጋሾች ደም ሲሰጡ በጥራት እና በብዛት ለተገልጋዮች እንዲደርስ ለደም ባንኮች መሳሪያዎች የሚያስፈልጉ በመኾናቸው ድጋፍ መደረጉን ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ደም ባንክ በኩል በበጎ ፈቃደኝነት ደም በሚለግሱ ወገኖች ብዙ ደም ፈላጊ እናቶችን እና ህጻናትን ሕይወት መታደግ መቻሉን ሚኒስትሯ ጠቅሰዋል። በቀጣይም በጎ ፈቃደኞች ልገሳቸውን በማጠናከር ለሰው ሕይወት መትረፍ መፍትሄ ሊሆኑ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በቀጣይም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ የደም እና ኅብረ ህዋስ ባንክ ጋር በመተባበር ደም ባንኮች ጥራት ያለው ደም ለተገልጋዮች እንዲያደርሱ እንሠራለን ብለዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየተፈጥሮ ሃብት ልማት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተጠናክሮ እንደሚከናወን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ገለጸ።
Next articleየተፋሰስ ልማት ሥራ በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን አርሶ አደሮች ተናገሩ።