
ጎንደር: ጥር 14/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ዩኒቨርስቲ የምሥረታ በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ነው። በዓሉ ከጥር 14/2017 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ድረስ 20 በሚኾኑ ሁነቶች ይከበራል።
በዩኒቨርስቲው የምስረታ በዓል ላይ ለመሳተፍ ጎንደር ከተማ የገቡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የጎንደር አብያተ መንግሥታት እድሳትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝት መርሐ ግብሩ የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፣ የጎንደር ዩንቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ.ር) ጨምሮ የመንግሥት ሥራ ኀላፊዎች፣ የዩኒቨርስቲው ማኅበረሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፦ ታዘብ አራጋው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
