ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በጎንደር ከውጭ ሀገር ጎብኝዎች ጋር መገናኘታቸውን ገለጹ።

52

ባሕርዳር: ጥር 12/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በጎንደር የጥምቀት በዓልን የታደሙ የውጭ ሀገራት ጎብኝዎችን ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በዓሉን በድምቀት የሚያከብሩ የውጭ የሀገር ጎብኝዎችን ማግኘት እና መቀበል አስደሳች ነበር ብለዋል።

የውጭ ሀገር ጎብኝዎች በዓሉ ወደር የለሽ መኾኑን እና በሕይወት አጋጣሚ ውስጥ እንድ ጊዜ የሚያገኙት እንደኾነ እንደነገሯቸውም ገልጸዋል። የጥምቀት አይነት በዓላት የኢትዮጵያን ታሪካዊ እና ባሕል እሴቶች የበለጠ እንደሚያበለጽጉም ፕሬዚዳንቱ አስፍረዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች የሚያጋጥማቸውን ችግር ለመፍታት እንደሚሠራ የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ገለጸ።
Next articleከከተራ እስከ ቃና ዘገሊላ ያሉ በዓላት በሰላም መጠናቀቃቸውን የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።