”ኢየሱስ ክርስቶስ ትህትናን እንዳስተማረ እኛም ጥያቄያችን ወደ እግዚአብሔር በትህትና ልናቀርብ ይገባል” ብጹዕ አቡነ ዘካርያስ

33

ፍኖተ ሰላም፡ ጥር 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የጥምቀት በዓል በፍኖተ ሰላም ከተማ ሃይማኖታዊ እና ባሕላዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት እየተከበረ ነው።

በጥምቀት በዓሉ ላይ የተገኙት የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ዘካርያስ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዮርዳኖስ ወርዶ ዮሐንስን አጥምቀኝ ባለው ጊዜ ‘ እኔ አገልጋይ ባሪያህ ነኝ እንጅ እንዴት አንተን ላጠምቅ እችላለሁ አለ’ በሚል ርዕስ ላይ ተነስተው ለአማኞቹ አባታዊ ትምህርት እና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል።

ብጹዕነታቸው በምስጢረ ጥምቀቱ የተገለጠው ነገርን ሁሉ በትህትና ማድረግ እንደሚገባን ነው ብለዋል።

ብጹዕ አቡነ ዘካርያስ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ትህትናን እንዳስተማረ እኛም ጥያቄያችን ወደ እግዚአብሔር በትህትና ልናቀርብ ይገባልም ነው ያሉት።

አሁን ላይም በባሕረ ጥምቀቱ ላይ ያደሩ ታቦታት በአማኞች እና በበዓሉ ታዳሚያን ታጅበው በሃይማኖታዊ እና ባሕላዊ ሥርአቶች ወደ መንበረ ክብራቸው እየተመለሱም ይገኛሉ።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article” እኛ ሰዎች መጥፎ ነገር በመሥራት በራሳችን ላይ ዕዳ ማምጣት የለብንም” መምህረ መምህራን የኔታ በጽሐ ዓለሙ
Next articleጥምቀት አንድነትን እና ትህትናን የሚያስተምር በመኾኑ ለሰላም እና ለአብሮነት እንደሚሠሩ በደብረ ማርቆስ የጥምቀቱ ታዳሚዎች ገለጹ።