የጥምቀት በዓል በአዳማ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው።

22

አዳማ ፡ ጥር 11/2017 ዓ.ም { አሚኮ} የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚከበር ደማቅ የዓደባባይ በዓል ነው።

ዛሬ እየተከወነ የሚገኘዉ የጥምቀት ሥርዓትም በአዳማ ከተማ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ጎርጎሪዮስ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ነው።

አሚኮ የጥምቀት በዓልን ሥነ ሥርዓት ከኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ እያደረሰ ነው። አሁን ላይ ሥርዓተ ጥምቀቱ እየተካሄደ ነው::

ዘጋቢ:- ሰለሞን አሰፌ-ከአዳማ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የጥምቀት በዓል ከመሠረቱ የሰላም ነጋሪት የታወጀበት፣ የፍቅር እምቢልታ የተነፋበት ነው” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
Next articleሥርዓተ ጥምቀት በባሕር ዳር በልዩ ድምቀት እየተካሄደ ነው።