የከተራ በዓል በቅዱስ ላሊበላ በድምቀት እየተከበረ ነው።

23

ባሕርዳር: ጥር 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የከተራ በዓል በቅዱስ ላሊበላ በድምቀት እየተከበረ ነው። ላሊበላ የከተራ እና የጥምቀት በዓላት በድምቀት ከሚከበሩቸው አካባቢዎች መካከል አንደኛዋ ናት።

የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ላሊበላ ጥምቀትንም በታላቅ መንፈሳዊ ሥርዓት ታከብራለች።

በከተራ በዓል ሥነ ሥርዓቱ የውጭ ሀገር እንግዶች በብዛት ታድመዋል። ታቦታቱ ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው በታላቅ አጀብ ጥምቀተ ባሕር ደርሰዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ጥምቀትን ሕዝበ ክርስቲያኑ ዘር እና ቀለም ሳይለዩ በአንድነት ማክበራቸው ሕዝብን ከማቀራረብ ባለፈ የመረዳዳት ባሕልን ያጎለብታል”
Next article” ጥንታዊ ሥልጣኔን ታሳቢ ያደረገ፣ ታሪክን ከግምት ያስገባ እና እሴትን የጠበቀ የሃሳብ ልዕልና ያስፈልጋል” ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ